Google search engine

ቅዳሜና እሁድ በተለያዩ አገራት በተካሄዱ የሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያዊያን ድል ቀንቷቸዋል

በተለያዩ የዓለም አገራት ቅዳሜና እሁድ በተካሄዱ የማራቶንና አገር አቋራጭ የአትሌቲክስ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን ውጤታማ ሆነዋል።
በዚሁ መሰረት በቻይና ሸንዤን በተካሄደ የሴቶች ማራቶን ሙሉ ሰቦቃ 1ኛ ስትሆን አሹ ቃሲም እና ደሲ ደቲ 3ኛና 4ኛ ሆነው መግባት ችለዋል።

በዚሁ የሸንዤን የወንዶች ማራቶን በቀለ ሙሉነህ፣ መላኩ አበራ፣ አሸናፊ ከተማና ኃይለሚካኤል መኮንን 2ኛ፣ 4ኛ፣ 5ኛ እና 7ኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ ሆነዋል።

በቱርክ መርሲን የሴቶች ማራቶንም ቆንጂት ጥላሁንና ጫልቱ ዲዳ 1ኛና 2ኛ በመውጣት አሸንፈዋል።

በመርሲኑ የወንዶች ማራቶን ደመቀ ካሳው አራተኛ በመሆን አጠናቋል።

በህንድ በተካሄደ የ25 ኪሎ ሜትር፣ በደቡብ አፍሪካ ግማሽ ማራቶን፣ በስፔን የ7 ነጥብ 6 እና የ8 ኪሎ ሜትር ውድድሮችም ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል ሲል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለኢዜአ ገልጿል።

spot_img
ተመሳሳይ ጽሁፎች

አስተያይት ያስፍሩ

እባክዎን አስተያይትዎን ያስፍሩ
እባክዎን ስምዎን እዚህ ያስገቡ

ትኩስ ዜናዎች

%d bloggers like this:
P